ETHIOPIANREPORTER.COM – ኢትዮጵያ ያልተጠቀመችበት የቱሪዝምና ጉዞ መድረክ

በዓለም በተለያዩ አገሮች የሚዘጋጁ ኮንፈረንሶች፣ ዓውደ ርዕዮችና ፌስቲቫሎች አገሮች ራሳቸውን ለማስተዋወቅና አገልግሎቶቻቸውን ለመሸጥ የሚጠቀሙባቸው ዓይነተኛ መድረኮች ናቸው፡፡

እንዲህ ዓይነቱን መድረክ መጠቀም የአንድን አገር ኢኮኖሚ ከማሳደግ ባለፈ፣ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለመፍጠርና ለመታወቅ ዕድል የሚሰጥ ቢሆንም፣ በተለይ ታዳጊ አገሮች ዕድሉን ብዙም ሲጠቀሙበት አይስተዋሉም፡፡ ኢትዮጵያም ከእነዚሁ ልትጠቀስ ትችላለች፡፡

ኢትዮጵያ የቱሪዝምና የጉዞ ኢንዱስትሪዋን ይበልጥ ለማስተዋወቅ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚዘጋጁ መድረኮች እምብዛም አለመገኘቷ፣ በዘርፉ በቅጡ እንዳትታወቅና ካላት የቱሪዝም ሀብት በብዛት እንዳትጠቀም ማድረጉን የፌስ ኦፍ ኢትዮጵያ ካልቸራል ኢቨንት ኦርጋናይዘርና ሥራ አስኪያጅ ደረጄ በለጠ ይናገራሉ፡፡

እሳቸው እንደሚሉት፣ ከዚህ ቀደም አሜሪካ፣ ደቡብ አፍሪካና በሌሎች አገሮች በተዘጋጁ የተለያዩ መድረኮች እምብዛም የኢትዮጵያን መንግሥት ወክሎ በቱሪዝሙ ዘርፍ የሚያስተዋውቅ አለመኖሩን መታዘብ ችለዋል፡፡ በእነዚህና በሌሎች መድረኮች መሳተፍ አለመቻሏም ኢትዮጵያን ካሏት የቱሪዝም ሀብቶች በብዛት እንዳትጠቀም እያደረገ ነው፡፡

መንግሥት ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የቱሪዝም ሀብት በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚዘጋጁ መድረኮች ተጠቅሞ ለማስተዋወቅ አቅሙ ባይኖረው እንኳን፣ ፍላጎትና አቅሙ ያላቸውና በግሉ ዘርፍ የተሰማሩ የዘርፉ ባለሙያዎች እንዲሳተፉ በኤምባሲና በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል ድጋፍ እንዲያገኙ በማበረታታት ተጠቃሚ መሆን የሚቻልበትን መንገድ ማመቻቸት ይገባዋል ይላሉ፡፡

Read More @ ethiopianreporter.com

Reviews

0 %

User Score

0 ratings
Rate This

Sharing

Leave your comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *