ADDISMALEDA.COM – የእኛን ሰውና ዱባይን በጨረፍታ

ኢትዮጵያዊያን ኑሮን ለማሸነፍ በዓለም ላይ በየአገሩ ተበትነዋል። ብዙዎች ተሳክቶላቸዋል፣ የሚልቁት ደግሞ ከአገራቸው ርቀውም የኑሮ ከባድ ትግል የተላቀቃቸው አይመስልም። ይህንን በዱባይ የሳምንት ቆይታው የታዘበው ታምራት አስታጥቄ፣ በክፍል ኹለት የጉዞ ማስታወሻው በዱባይ ያለውን የኢትዮጵያዊያንን ኑሮና መልክ በጥቂቱ አንስቶ፣ ካየውና ከሰማው አካፍሎናል። በዱባይ የሚገኙ ድንቅ የሚባሉ መስህቦችንም አስቃኝቶናል።

ኢትዮጵያዊያን በዱባይ

ኦሪት መሐመድ ከምሥራቁ የአገራችን ክፍል ሐረር የተገኘች ኢትዮጵያዊት ናት። በሰሜን አሜሪካ የማስትርስ ዲግሪዋን በልማት ላይ ትኩረት ባደረገው ‹ፐብሊክ ፖሊሲ› የትምህርት ዘርፍ አጠናቅቃ ወደ ኢትዮጵያ በተመለሰች በሦስተኛ ወሩ ነዋሪነቱ ዱባይ ከሆነው ከያኔው ፍቅረኛዋ ከአሁኑ ባለቤቷ እና የሦስት ልጆቿ አባት ጋር የመተዋወቅ ዕድል ገጠማት። ከጋብቻ በኋላ እሷም ጠቅልላ ዱባይ ላይ ከተመች።

ገና ከርቀት ለሚያያት ፊቷ ጥርስ በጥርስ የምትባልና ፈገግታዋ ከፊቷ ላይ የማይጠፋ ናት፣ እንደውም የሚጋባ፣ በቀላሉ ተግባቢና ተጫዋች ናት። ኦሪት በዐስራ ኹለት ዓመታት የዱባይ ቆይታዋ ጥሬ ቡና ከኢትዮጵያ በማስመጣትና በመቁላት ቁጥር አንድ ተመራጭ የሆነ ‹ቡን ኮፊ› የተሰኘ የቡና ብራንድ ፈጥራለች። ከዛም ባሻገር በዱባይ ብቻ ሰባት ካፌዎች በመክፈት ተቆልቶ የተፈጨና በተለያየ መጠን የተዘጋጀውን መግዛት፤ አልያም በካፌዎቹ ውስጥ የተዘጋጁትን ከነእፍታቸው መጠጣት ይቻላል።

Read More @ addismaleda.com

Reviews

0 %

User Score

0 ratings
Rate This

Sharing

Leave your comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *